image
image
image
image
image

በህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራ ፍትሐዊ የፋይናንስ አሰባሰብን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ።

ታህሳስ 7, 2017
የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከሁሉም ወረዳ ለተውጣጡ የቅጥር ጥበቃና የኮሚኒት ፖሊስ አባላት በቅጥር ጥበቃ መመሪያ 144/2016 እና በፋይናንስ መመሪያ 20/2015 የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሂዷል። መድረኩን የመሩት የክ/ከተማው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሪት ሐብታሟ ቡልቻ በህብረተሰብ ተሳትፎ ሥራ ፍትሐዊ የፋይናንስ አሰባሰብን ለማረጋገጥና የሐብት ብክነት እንዳይሰት ለመከላከል በቅጥር ጥበቃ መመሪያ 144/2016 እና በፋይናንስ መመሪያ 20/2015ን በመከተል በትክክል እንዲሠራበት የሚታዩ የክህሎት ክፍተቶችን ለመሙላት እንዲረዳ የተሰጠ የግንዛቤ ማስጨበጫ ነው ብለዋል። የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ በበኩላቸው የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የቅጥር ጥበቃ አደረጃጀት ሁነኛ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል። በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ መመሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጳውሎስ ተመስገን በበኩላቸው የነዋሪዎችን ሁሉንተናዊ ደህንነትና እንቅስቃሴ ሰላማዊ መንፈስ ለመፍጠር በህዝብ አጋዥነት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነትና የህዝብ አደራን በአግባቡ ለመወጣት ጠንክረው እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች