image
image
image
image
image

ወጣቶች ለጠንካራ ሃገረ መንግስት ግንባታ መሳካት ጉልህ ድርሻ ያላቸው በመሆኑ በሰላም ጉዳይ ከመንግስት ጋር ተቀናጅተው እየሰሩ መሆናቸው ተገለፀ::

ህዳር 18, 2017
በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ከሚገኙ ወጣቶች በወቅታዊ የሰላምና ፀጥታ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል፡፡ መድረኩን የመሩት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ምክትልና ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አብነት አሰግድ የወጣቶችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ እቅዶች ተነድፈው ተግባራዊ በመደረግ ላይ መሆኑን ጠቅሰው ወጣት ለሃገር ግንባታም ሆነ ለማህበረሰባዊ ተጠቃሚነት መረጋገጥ ጉልህ ሚና ያለው በመሆኑ ከመንግስትና ህዝብ ጋር ተናቦና ተቀራርቦ መስራት ይገባል ሲሉ ገልፀዋል፡፡ የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ በበኩላቸው ወጣቶች በሃገረ መንግስት ግንባታ ሂደት የማይተካ ሚና ያላቸው በመሆኑ ሃገራችን የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማስቀጠል እያደረጉት ያለውን ተሳትፎ አጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡ በውይይት መድረኩ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት እስታፍ አባሎ ኮሎኔል ግርማይ የተገኙ ሲሆን የአካባቢን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ወጣቶች እንደሁልጊዜውም የሚያደርጉትን ጥረት አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸውም በመድረኩ ተገልጿል::

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች